18 January, 2012
ኢትዮጵያ ውስጥ አምስት የውጭ ቱሪስቶች ተገደሉ
በኢትዮጵያ የአፋር ክልል አምስት አውሮፓዊያን ሀገር ጎብኚዎች ማንነታቸው ባልታወቀ ታጣቂዎች ተገድለዋል።
ፎቶ፡ N/A
የኤርታ አሌ አካባቢ በካርታ ላይ
አምስቱ ቱሪስቶች ሰኞ ዕለት የተገደሉትና ሌሎች ሁለት አብረዋቸው የነበሩ የተጠለፉት በክልሉ በጎብኚዎች መስኅብነት በሚታወቀውና ኤርትራና ኢትዮጵያ በሚዋሰኑበት አቅራቢያ በሚገኘው በኤርታ አሌ እሳተ ገሞራ አካባቢ ሲንቀሳቀሱ በነበረበት ወቅት መሆኑ ተዘግቧል።
“ጥቃቱ የኤርትራ ድርጊት ለመሆኑ ጥርጣሬ የለኝም” ሲሉ በኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የፐብሊክ ፕሮሞሽንና ኮምዩኒኬሽን ዳይሬክተር ጄኔራል አቶ ጌታቸው ረዳ ከስሰዋል፡፡
የኤርትራው የማስታወቂያ ሚኒስትር አቶ አሊ ዓብዶ በሰጡት ምላሽ ክሱን ውድቅ አድርገዋል።
ዝርዝሩን ያዳምጡ፡፡
- Listen: ኢትዮጵያ ውስጥ አምስት የውጭ ቱሪስቶች ተገደሉ
MP3
VOA 60 - Africa
To view our site properly you may need to install the Geez font : Download Now
If you are still having problems viewing our site you may need to change your browser settings. FAQ: Update Browser Settings